በግጭት ምክንያት ከቀያቸው የሚፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከ100 ሚሊየን ማለፉ ተገለጸ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የተመድ የሥደተኞች ኮሚሽን በግጭቶች አስገዳጅነት ከቀያቸው የሚፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ለመጀመሪያ ጊዜ ከ100 ሚሊየን ማለፉን አስታወቀ፡፡
በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል የተከሰተው ጦርነት የሥደተኞችን ቁጥር ከ100 ሚሊየን እንዲልቅ እንዳደረገው ኮሚሽኑ ማስታወቁን ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል፡፡