የማዕከሉ ሀላፊ አቶ ቦና ሂርጳ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት፥ ተምቹ በወረዳው በሚገኙ አራት ቀበሌዎች ተከስቷል።
በዚህም በ400 ሄክታር መሬት ላይ በሚገኝ የበቆሎ፣ጤፍ፣ማሽላ፣ ዳጉሳ እና የግጦሽ ሳር ላይ ጉዳት አድርሷል ነው ያሉት፡፡ አሁን ላይ ተባዮችና የዕፅዋት በሽታዎች እየተስፋፉ በመሆኑ አርሶ አደሩ ማሳውን በመፈተሽ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡
በተመስገን አለባቸው