ባለፉት ዘጠኝ ወራት በማዕድን ዘርፍ ከ458 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ
ማዕድን ሚኒስቴር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያስመዘገባቸው ውጤቶች አስቸጋሪ በሆነ ሀገራዊ እና ለዘርፉ ፈታኝ በሆነ ሁኔታ ውስጥ መሆኑም በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡
በተለይም የዘርፉ የስራ ሁኔታ ለፀጥታ ስጋትና ችግሮች ቀጥተኛ ተጋላጭ በመሆኑ÷ በአብዛኛው የማዕድን ምርት ባለባቸው አካባቢዎችና ኩባንያዎች በከፊልና ሙሉ በሙሉ ምርት እንዲያቆሙ መደረጋቸውም ተገልጿል፡፡
ያም ሆኖ የወጪ ንግድ ማዕድናትን የምርት መጠን ለማሳደግ ልዩ የድጋፍ፣ የክትትልና የቁጥጥር ስርዓት በተመረጡ አካባቢዎች በመተግበሩ÷ አፈፃፀሙን ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት የተሻለ ማድረግ ተችሏል ነው የተባለው።