የሀገር ውስጥ ዜና

ቀጠናውን በአትሌቲክስ ብቻ ሳይሆን በጥበባት እና በባህል ፌስቲቫልም የሚታወቅ እናደርገዋለን-አቶ ደመቀ መኮንን

By Feven Bishaw

May 24, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)ቀጠናውን በአትሌቲክስ ብቻ ሳይሆን በጥበባት እና በባህል ፌስቲቫልም የሚታወቅ እናደርገዋለን ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ፡፡

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባባር ከሰኔ 7 እስከ 12 2014ዓ.ም የምስራቅ አፍሪካ የጥበባትና የባህል ፌስቲቫል በአዲስ አበባ አዘጋጅቷል፡፡

ይህንንም  ቀጠናዊ ፌስቲቫል ለማሳካት ከአጋርና ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡

 

የምስራቅ አፍሪካ የጥበባትና የባህል ፌስቲቫልም የሙዚቃ፣ የፊልም፣ የስዕልና ቅርጻ ቅርጽ ፌስቲቫል፣ የመጻሕፍትና የዕደ ጥበባት ዐውደ ርዕይ፣ የሲምፖዚየም እና የስፖርት ፌስቲቫሎችን በውስጡ የያዘ መሆኑን አመላክተዋል፡፡