ስፓርት

የዓለም ዋንጫ አዲስ አበባ ገባ

By Feven Bishaw

May 24, 2022

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 16 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ2022ቱ የኳታር የዓለም እግር ኳስ ውድድር አስቀድሞ በተለያዩ ሀገራት ለእይታ የሚቀርበው የዓለም ዋንጫ ዛሬ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡

ብራዚላዊው የባርሴሎና የቀድሞ የቀኝ መስመር ተከላካይ በጁሊያኖ ቤሌቲ ዋንጫውን ይዞ አዲስ አበባ ገብቷል።