አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ማዕከላዊ ዕዝ ሀገርን ሊያሸብር የሚያስብ ማናቸውንም የጠላት ኃይል መደምሰስ የሚያስችል ወታደራዊ አቅም መገንባቱን የዕዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጀነራል ዘውዱ በላይ ገለጹ፡፡
ማዕከላዊ ዕዝ በተለያየ የመሬት ገፅታ ላይ ሊያጋጥም የሚችል ጠላት ላይ ድል ለመቀዳጀት እና ለመደምሰስ የሚያስችለውን ወታደራዊ ልምምድ ማድረጉን ሌተናል ጀነራል ዘውዱ ተናግረዋል፡፡