የሀገር ውስጥ ዜና

የአፍሪካ ወጣቶች የአህጉሪቱን ችግሮች በመጋፈጥ መፍትሄያቸው ላይ ሊያተኩሩ ይገባል- አቶ ደመቀ መኮንን

By Feven Bishaw

May 25, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ወጣቶች የአህጉሪቱን ችግሮች በመጋፈጥ መፍትሄዎቻቸው ላይ ሊያተኩሩ እንደሚገባ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ።

የ2022 የፓን አፍሪካ ወጣቶች ስብሰባ በአዲስ አበባ በዛሬው ዕለት መካሄድ ጀምሯል፡፡