የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ ከኮካ ኮላ ኩባንያ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

March 05, 2020

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 26 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኮካ ኮላ ኩባንያ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ተወያዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኮካ ኮላ ሊቀ መንበር ጄምስ ኩይንሲ እና የኮካ ኮላ ኩባንያ የአፍሪካ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጃኩዬስ ቨርሚዩለን ጋር ነው የተወያዩት።

በውይይታቸው ወቅትም ኮካ ኮላ በመጭው ክረምት በሃገር አቀፍ ደረጃ ለመትከል ለታቀደው የ5 ቢሊየን ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጧል።

ከዚህ ባለፈም በኢትዮጵያ መጠነ ሰፊ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ ለማድረግ ቃል መግባቱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል።

Glad to have met James Quincy & Jacques Vermeulen of @CocaColaCo. I welcome their commitment to expand investments and support our city dev’t projects. They also affirmed support to our 5bil trees goal in the upcoming season & to mobilize large scale investments in #Ethiopia. pic.twitter.com/vAkKVcDudU

— Abiy Ahmed Ali 🇪🇹 (@AbiyAhmedAli) March 5, 2020

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት ኮካ ኮላ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋትና በአዲስ አበባ እየተተገበሩ ላሉ ፕሮጀክቶች የሚያደርገውን ድጋፍ አድንቀዋል።

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ! https://t.me/fanatelevision