የሀገር ውስጥ ዜና

ዶ/ር ሊያ ከኖርዌይ አቻቸው ጋር ጤናን እና የጤና መረጃ ስርዓትን በቴክኖሎጂ መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያዩ

By Feven Bishaw

May 26, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ከኖርዌይ አቻቸው ኢንግቪልድ ጀርኮል ጋር ጤናን እና የጤና መረጃ ስርዓትን በቴክኖሎጂ መደገፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።

በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ካለው 75 ኛው የዓለም ጤና ጉባኤ ጎንለጎን የሁለቱ አገራት ሚኒስትሮች በተለይም ጤናን እና የጤና መረጃ ስርዓትን በቴክኖሎጂ መደገፍ፣ አቅም ገንቢ ጥናትና ምርምር እንዲሁም የእውቀት ልውውጥ ዙሪያ ላይ መክረዋል።