አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ሐብታሙ ኢተፋ በኢትዮጵያ ከህዋዌ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጋር የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱን የኢንፎርሜሽን ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶች ለማዘመን በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ጋር ተወያዩ፡፡
ሚኒስቴር መሥሪየ ቤቱ የኢንፎርሜሽን ኮምዩኒኬሽን መሠረተ ልማቱን ማዘመንና የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ መረጃዎችን ለተጠቃሚዎች ለማቅረብና አሠራሩን ለማቀላጠፍ ፍላጎት እንዳለው ነው ሚኒስትሩ በውይይቱ የተናገሩት፡፡