ቢዝነስ

10ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ባዛርና አውደ ርዕይ ተከፈተ

By Tibebu Kebede

March 05, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 26፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) 10ኛው የአዲስ አበባ ከተማ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ባዛርና አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ኤግዚቪሽን ማዕከል በዛሬው ዕለት ተከፍቷል።

በመክፈቻ ስነ ስርዓቱ ላይ በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የመንግስት አገልግሎት ሰጭ ተቋማት አስተባባሪ ኢንጅነር እንዳወቅ አብጤ እና የአዲስ አበባ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጋቱ ዳኛቸውን ጨምሮ የተለያዩ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።