አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከውጭ የሚገባን የአፈር ማዳበሪያ እስከ 20 በመቶ የሚሆነውን ጉድለት መሙላት የሚችል የተፈጥሮ ማዳበሪያ ላይ እየተሰራ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡፡
የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ÷ ኮምፖስትን ጨምሮ የአፈር ለምነትን የሚጨምሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ላይ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።