Fana: At a Speed of Life!

“ከወንድሜ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል” – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) “ እንደወትሮው ሁሉ ከኬንያው ፕሬዚዳንት ከወንድሜ ኡሁሩ ኬንያታ ጋር  ውጤታማ ውይይት አድርገናል” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

 

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ጋር በሁለትሽ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

 

በውይይታቸውም  በሁለትዮሽ የሰላምና ልማት ጉዳዮች እንዲሁም በባለብዙ ወገን በቀጠናው ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል፡፡

 

ውይይታቸው  ውጤታማ እንደነበር ገልፀው፥  ለተደረገላቸው ወንድማዊ አቀባበልም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ  ምስጋና አቅርበዋል።

 

በኬንያ ለሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፥ ናይሮቢ ከተማ ውስጥ በአገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት በተዘጋጀው የአየር ትርዒት ፌስቲቫል ላይ መታደማቸውን የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የአየር ትርዒቱ በናይሮቢ ከተማ በኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ቅጥር ጊቢ ውስጥ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በትርዒቱም በሺዎች የሚቆጠሩ ኬንያውያን መታደማቸውም ታውቋል፡፡

 

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.