የሀገር ውስጥ ዜና

ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በ18 ወራት ውስጥ ግንባታው የተጠናቀቀውን የገርጂ ዘመናዊ የመኖሪያ መንደር ጎበኙ

By Feven Bishaw

May 28, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፣ የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ እና የፌዴራል ፖሊስ ኪሚሽን ምክትል ኮሚሽነር መላኩ ፈንታ የአልሙኒየም ፎርምወርክ የግንባታ ቴክኖሎጂ ውጤት የሆነውን የገርጂ ዘመናዊ የመኖሪያ መንደርን ጎብኝተዋል።

የገርጂ ዘመናዊ የመኖሪያ መንደር፥ ዘመናዊ የግንባታ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በ18 ወራት ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ ማጠናቀቅ የቻለና በኢትዮጵያ የግንባታ ኢንዱስትሪ ውስጥ አዲስ ታሪክ ያስመዘገበ ግዙፍ መንደር መሆኑ ተገልጿል።