የሀገር ውስጥ ዜና

ጠ/ሚ ዐቢይ ከአዲስ አበባ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ጋር በመሆን ከተማዋን አጽድተዋል

By Tibebu Kebede

March 06, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከአዲስ አበባ የብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ጋር በመሆን በመዲናዋ የጽዳት ዘመቻ አካሂደዋል።

የጽዳት ዘመቻው “ቆሻሻ አስተሳሰብን እና ቆሻሻን ከከተማዬ አጸዳለሁ” በሚል መሪ ቃል ነው በዛሬው እለት የተካሄደው።