የሀገር ውስጥ ዜና

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የስራ ቦታ ላይ ክትትል ለማድረግ ያስችላል የተባለውን የሰራተኞች የጣት አሻራ ፊርማ አሰራርን አስጀመሩ

By Feven Bishaw

June 03, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሰራተኞች የመንግስት የስራ ሰዓትን በአግባቡ እንዲጠቀሙ ለማስቻል የጣት አሻራ ፊርማ የማስጀመር ስነ ስርዓት በአዲስ አበባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ተካሂዷል፡፡

በመርሃ ግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፥ በከተማ አስተዳደሩ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመንና ፈጣን ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ ከንቲባዋ የልደታ ክፍለ ከተማን አገልግሎት አሰጣጥ፤ የከተማ ግብርና፤ የዳቦ ፋብሪካዎች እና የምገባ ማዕከላት ግንባታ፤የቤት ግንባታ፤  እንዲሁም የሌሎች ፕሮጀክቶችን አፈጻጸፀም  ጎብኝተዋል ።

 

በክፍለ ከተማው  እየተከናወኑ ያሉ ግንባታዎችና ሌሎች ሰው ተኮር ተግባራት በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁም ከተማ አስተዳደሩ እንቅፋት የሚሆኑ ችግሮችን   በመለየት   በተለየ ሁኔታ ድጋፍ እንደሚደረግ ተናግረዋል ።

 

ከንቲባ አዳነች  ከፕሮጀክቶች ጉብኝት ጎን ለጎን በወረዳዎች ያለውን በአገልግሎት ዘርፉን የሚታዩ  ችግሮችን  የተመለከቱ ሲሆን÷ አገልግልግሎት ፈልገው ከመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት አካሂደዋል፡፡