የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ የመጥፋት አደጋ የተደቀነባቸው ቋንቋዎችን ለማበልጸግ እየተሰራ ነው

By Feven Bishaw

June 06, 2022

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የመጥፋት አደጋ ስጋት የተደቀነባቸውን ቋንቋዎች በመለየት የመሰነድና እንዳይጠፉ የማበልጸግ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ባህሎች አካዳሚ አስታወቀ።

አካዳሚው 50ኛ ዓመት የጥናትና ምርምር ጉዞውን የሚዘክር ክብረ-በዓል የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አመራሮችና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ አክብሯል።