Fana: At a Speed of Life!

ወ/ሮ መሠረት ዳምጤ የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 2 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 6ዙር 1ኛ ዓመት 12ኛ መደበኛ ጉባዔ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የቀረቡለትን የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር እና ምክትል ዋና ኦዲተር ሹመት በሙሉ ድምፅ አጽድቋል።

በዚህም ወይዘሮ መሠረት ዳምጤ ጫንያለው የፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር እንዲሁም አቶ አበራ ታደሰ ኢትቻ ደግሞ ምክትል ዋና ኦዲተር ሆነው ተሾመዋል።

ተሿሚዎቹ በምክር ቤቱ አባላት ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ መፈፀማቸውን ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.