የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ላይ የሚሰራጩ ግጭት-ቀስቃሽ የጥላቻ ንግግሮችን ፌስቡክ መቆጣጠር አለመቻሉን ጥናት አመላከተ

By Feven Bishaw

June 10, 2022

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በፌስቡክ የሚሰራጩ የጥላቻ ንግግሮችን ኩባንያው መቆጣጠር አለመቻሉን ወይም አለመፈለጉን በማይናማር እና በኢትዮጵያ ላይ የተካሄደ ጥናት አመለከተ።

በፌስቡክ የተሰራጩ ግጭት ቆስቋሽ የጥላቻ መልዕክቶች በማይናማር ጅምላ ጭፍጨፋ ማስከተላቸውንና ኢትዮጵያም በፌስቡክ በኩል የተሰራጩ የጥላቻ ንግግሮች ሰለባ መሆኗን የተካሄደው ጥናት አብራርቷል።