አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሚካኤል ሀመርን ጋር ተወያይተዋል ።
በውይይታቸውም በሰሜን የኢትዮጵያ ክፍል በግጭት ለተጎዱ አካባቢዎች የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦትን እንዲሁም በግጭቱ ወቅት ለተፈጸሙ በደሎች ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እየተወሰዱ ባሉ እርምጃዎች እና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።