አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቀጣዮቹ አስር ቀናት በደቡብ ምዕራብና በምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች የተሻለ ዝናብ ሊኖር እንደሚችል የኢትዮጵያ ሚቲዮሮሎጂ ኢኒስቲትዩት አስታወቀ፡፡
በዚህም በሚቀጥሉት አስር ቀናት ለዝናብ መፈጠር አስተዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዮሮሎጂ ገጽታዎች እየተጠናከሩ ሊሄዱ እንደሚችሉና በተለይም በደቡብ ምዕራብና በምዕራብ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት ሊኖር እንደሚችል ነው የተገለፀው፡፡