አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል አመራሮችን ጨምሮ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች በባህርዳር ከተማ የተገነቡና በመገንባት ላይ ያሉ ትልልቅ መሰረተ ልማቶችን ጎብኝተዋል፡፡
የባህርዳር ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ዶክተር ድረስ ሳህሉ በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት÷ የባህርዳርን ልማት ሁለንተናዊና ተደራሽ ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ ከራሱና ከዓለም ባንክ በሚመደብ የመቀናጆ በጀት ሰፊ ስራ እየተሰራ ነው።