አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ በተያዘው በ2014ዓ.ም ክረምት የአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር ከ7 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ችግኝ ለመትከል በዘጠኝ ችግኝ ጣቢያዎች ችግኝ የማፍላት የቅድመ ዘግጅት መደረጉን አስታወቀ፡፡
አስተዳደሩ እንዳለው ፥ እስካሁን ከ1 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ የችግኝ የጉድጓድ ቁፋሮ የቅድመ ዝግጅት ስራ ተጠናቋል፡፡