አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋዜጠኝነት ሙያ እና ማህበረሰብን የማንቃት እንቅስቃሴ የሚና መደበላለቅ ችግር እየፈጠረ በመሆኑ ድንበር ሊበጅለትና በሕግ ሊመራ ይገባል ሲሉ የዘርፉ ባለሙያዎች ተናገሩ፡፡
የሚዲያ ልማት ባለሙያው አቶ ሄኖክ ሰማእግዜር ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ የየራሳቸው ሙያዊ ሥነ ምግባርና መርሆ ያላቸው ጋዜጠኝነት እና የማህበረሰብ አንቂነት በመርህ ሊመሩና በአግባቡ ስራ ላይ ሊውሉ ይገባል፡፡