የሀገር ውስጥ ዜና

አምባሳደር አወል ከባህሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ጋር ስለሰራተኞች ስምሪትና ደህንነት ጉዳይ ተወያዩ

By Feven Bishaw

June 15, 2022

አዲስ አበባ፣ሰኔ 8፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በባህሬን የኢትዮጵያ ቆንስል ጄኔራል አምባሳደር አወል ወግሪስ መሀመድ ከባህሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሥራ ኃላፊዎች ጋር ስለሰራተኞች ስምሪትና ደህንነት ጉዳይ ተወያዩ፡፡

አምባሳደሩ የሹመት ደብዳቤቸውን በባህሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር የቆንስላዎችና የአስተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ተጠባባቂ ሃላፊ ለሆኑት ለአምባሳደር ኸሊል ያቆብ አል-ኻያት አቅርበዋል።