በጦር መሣሪያ በመታገዝ የዘረፋ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በ19 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
በሌላ በኩል በሲዳማ ክልል በሙስና ወንጀል የተከሰሰ ተከሳሽ በገንዘብና በጽኑ እስራት ተቀጥቷል፡፡
ተከሳሽ ታደሰ ሪቅዋ የተባለው የቦሪቻ ወረዳ ነዋሪ አላግባብ ጥቅም ለማግኘት ሐምሌ 19 ቀን 2013 ዓ.ም ሃሰተኛ የባንክ ስሊፕ በመጠቀም 36 ነጥብ 5 ኩንታል ስኳር ከሲዳማ ኤልቶ ገበሬዎች ዩኒዬን ወጪ በማድረግ ለግል ጥቅም አውሏል ተብሏል፡፡
ግለሰቡ የሙስና ወንጀል አዋጅ 881/2007 አንቀጽ 23(3) ላይ የተገለጸውን ህግ በመተላለፉ የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በቀን የካቲት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ክስ መስርቶበታል፡፡
በተከሳሽ ላይ የቀረበውን ክስና ክሱን ለማረጋገጥ የቀረቡትን የሰነድና የሰው ማስረጃዎችን ሲያጣራ የቆየው የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰኔ 9 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽን ጥፋተኛ በማለት የሶስት አመት ጽኑ እስራትና የሶስት ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጣ መወሰኑን ከክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።