አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በምርጫ ወቅት የሚነሱ አለመግባባቶችና ክርክሮች አፈታትን በማስመልከት አውደ ጥናት እያካሄዱ ነው፡፡
አውደ ጥናቱ በመጪው ነሃሴ ወር በሚከናወነው ሀገር አቀፍ ምርጫ ወቅት ፍርድ ቤቶች የሚኖራቸውን ሚና እና የህግ ማዕቀፎችን ማስተዋወቅ እንዲሁም ከዳኞች ጋር ምክክር ማካሄድ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡