የሀገር ውስጥ ዜና

በምርጫ ወቅት የሚነሱ አለመግባባቶችን መፍታት በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ያተኮረ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው

By Tibebu Kebede

March 07, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በምርጫ ወቅት የሚነሱ አለመግባባቶችና ክርክሮች አፈታትን በማስመልከት አውደ ጥናት እያካሄዱ ነው፡፡

አውደ ጥናቱ በመጪው ነሃሴ ወር በሚከናወነው ሀገር አቀፍ ምርጫ ወቅት ፍርድ ቤቶች የሚኖራቸውን ሚና እና የህግ ማዕቀፎችን ማስተዋወቅ እንዲሁም ከዳኞች ጋር ምክክር ማካሄድ ያለመ መሆኑ ተገልጿል፡፡