ቢዝነስ

አማራ ባንክ በዛሬው ዕለት ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀመረ

By Mekoya Hailemariam

June 18, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር በዛሬው ዕለት ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀምሯል።

የአማራ ባንክ አክሲዮን ማህበር የምረቃ እና ስራ ማስጀመሪያ ስነ ስርዓት በዛሬው ዕለት ለገሃር በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ተካሂዷል።

 

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሄኖክ ከበደ በበኩላቸው፥ አማራ ባንክ የተቀናጁ ሀሳቦች እና የተባበሩ እጆች የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ውጤት ሆነው የተመሰረተ ባንክ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ባንኩን እውን ለማድረግ እና ሥራ ለማስጀመር ውጣ ውረድ እንደነበረ ገልፀው፥ ተቋሙ የታለመለትን ዓለማ ከግብ ያደርስ ዘንድ በቁርጠኝነት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል፡፡

የተቀመሩትን የባንኩን እሴቶች በማጉላት በፋይናስ ኢንዱስትሪው ውስጥ ባንኩ ቃሉን ከተግባር ጋር የተገናኘ እንዲሆን በሙሉ ልብ ገበያውን በመቀላቀል የኢንዱስትሪ ጉልበት ለመሆን እንሠራለን ብለዋል፡፡

ሀገሪቱ የጀመረችውን ልማት ለማፋጠንም ከቀደሙ ባንኮች ልምዶችን በመውሰድ፣ ዘመኑን የዋጁ የባንክ ስርዓቶችን ቀምሮ በመተግበር በዘርፉ ልምድ ያካበቱ ባለሙያዎችን በማሳተፍ የተሸለ እና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመውጣት በቅንጅት እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡