የሀገር ውስጥ ዜና

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የማዕድን ሃብትን በዘላቂነት ለማልማት ያለመ የማዕድን ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው

By Feven Bishaw

June 18, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኝ የማዕድን ሃብትን በዘላቂነት ለማልማት ያለመ የመጀመሪያው ክልል አቀፍ የማዕድን ሲምፖዚየም እየተካሄደ ነው።

“የማዕድን ሀብት ለዘላቂ ልማት” በሚል መሪ ሃሳብ እየተካሄደ የሚገኘው ሲምፖዚየም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል አመራሮች፣ ተመራማሪዎች፣ በዘርፉ የተሠማሩ ባለሃብቶችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።