የሀገር ውስጥ ዜና

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀን በአዲስ አበባ ተከበረ

By Tibebu Kebede

October 25, 2019

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት13፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2019 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀን በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ አፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ቅጥር ግቢ ውስጥ ተከብሯል።

በበዓሉ  የተመድ ምክትል ዋና ፀሀፊ አሚና መሃመድ፣ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት  ተወካዮችና ዲፕሎማቶች ተገኝተዋል።

በአከባበር ስነ ስርዓቱ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሰንደቅ ዓላማ የመስቀል መርሃ ግብር ተከናውኗል።