የሀገር ውስጥ ዜና

የኃይለማሪያምና ሮማን ፋውንዴሽን በሐመር እና በናፀማይ ወረዳዎች ሥራ ጀመረ

By Feven Bishaw

June 23, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የኃይለማሪያምና ሮማን ፋውንዴሽን በደቡብ ኦሞ ዞን በሐመር እና በናፀማይ ወረዳ የሴቶችን የትምህርት ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማሳደጊያ ፕሮጀክትን የፋውንዴሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ በይፋ አስጀምረዋል፡፡

ወይዘሮ ሮማን በመርሐ ግብሩ ÷ለሴት ተማሪዎች የማጣቀሻ መጽሐፍትና ሌሎች ግብዓቶችን በስጦታ መልክ ያበረከቱ ሲሆን÷ የሴት ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት አሰጣጥ ሁኔታን በመጎብኘት ከተማሪዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡