በኢትዮጵያ የአውሮፓ ሕብረት አምባሳደር ሮላንድ ኮቢያን በበኩላቸው÷ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድና ሪፈራል ሆስፒታል ባደረጉት ጉብኝት በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ዜጎች እንደተመለከቱ ተናግረዋል፡፡
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አሸናፊ ታዘበው እንደገለጹት÷ ሆስፒታሉ በዚህ ዓመት ብቻ በጦርነት ጉዳት ከደረሰባቸው ወገኖች ውጪ ከ400 ሺህ በላይ ተመላላሽና ከ35 ሺህ በላይ ተኝተው የሚታከሙ ህሙማንን አስተናግዷል፡፡
የአውሮፓ ሕብረት ልዑክ ሆስፒታሉ እየሰጠ ያለውን አገልግሎትና ያለበትን ችግር እንደተመለከተ እና በቀጣይ አስፈላጊ ድጋፎች በሚደረግባቸው ጉዳዮች ላይ ምክክር መደረጉንም ጠቁመዋል፡፡
በሙሉጌታ ደሴ