የሀገር ውስጥ ዜና

የዓለም የምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች የሰብአዊ ድጋፍ ለማጠናከር በትጋት እየሰራ መሆኑን ገለጸ

By Feven Bishaw

June 23, 2022

አዲስ አበባ፣ሰኔ 16፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከአለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቤስሊ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም አምባሳደር ሬድዋን የሰብዓዊ ጉዳዮችን ጨምሮ በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ለዋና ዳይሬክተሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡