የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮ-ጣሊያን የቢዝነስ ፎረም ተጠናቀቀ

By Feven Bishaw

June 25, 2022

 

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ትኩረቱን በኢንቨስትመንት፣ በንግድና በቱሪዝም ላይ ያደረገው የኢትዮ-ጣሊያን የቢዝነስ ፎረም መጠናቀቁን በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ገለጸ፡፡

በኤምባሲው አዘጋጅነትና በኮፊ ኢንዱስትሪያል አፍሪካና ሜዲትራኒያን እንዲሁም በቦንለይ ኤረዲ የህግ አማካሪ ድርጅት ተባባሪነት የተዘጋጀው የቢዝነስ ፎረሙ ለሁለት ቀናት በሮም ተካሄዷል።