የሀገር ውስጥ ዜና

በሰዎች የመነገድ ድርጊት ለመከላከል የ“ሰማያዊ ልብ” የግንዛቤ መፍጠሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ

By Tibebu Kebede

October 25, 2019

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በሰዎች የመነገድ ድርጊትን ለመከላከል እና በህብረተሰቡ ላይ የሚያደርሰውን ጫና መቀነስ የሚያስችል ዓለም አቀፍ የግንዛቤ መፍጠሪያ መርሃ ግበር ተካሄደ።

“ሰማያዊ ልብ” በሚል መሪ ቃል የተካሄደው የግንዛቤ መፍጠሪያ ዘመቻው በዛሬው እለት በሚሌኒየም አዳራሽ ተካሂዷል።