የሀገር ውስጥ ዜና

በደቡብ ክልል በዘንድሮው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ1 ነጥብ 8 ሚሊየን በላይ ወጣቶች ይሳተፋሉ

By Feven Bishaw

June 27, 2022

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በደቡብ ክልል በዘንድሮው የክረምት ወቅት የወጣቶች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ1 ነጥብ 8 ሚሊየን በላይ ወጣቶች እንደሚሳተፉ ተገለጸ፡፡

በተያዘው የክረምት ወራት በሚካሔደው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት አስተዋጽኦ ለማበርከት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ወጣቶች ፌደሬሽን አስታውቋል ፡፡