አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ እና በቅርቡ የቻይና ኮሚዩኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ሊዩ ጂያንቾኦ የዌብናር ውይይት አድርገዋል፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ ለቻይና ኮሚዩኒስት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ሚኒስትር ሊዩ ጂያንቾኦ፥ ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ፣ ስለ አረንጓዴ አሻራ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ገለጻ አድርገውላቸዋል።