አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጃፓን ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ አጠናክራ እንደምትቀጥል የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ አረጋገጡ።
የኢፌዲሪ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሙላቱ ተሾመ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የተላከ ልዩ መልዕክት በዛሬው እለት ለጃፓኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ማስረከባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።