አዲስ አበባ፣ መጋቢት 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ልክ የዛሬ አንድ ዓመት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737 አውሮፕላን ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ በመብረር ላይ እያለ ድንገት ተከሰከሰ።
የበረራ ቁጥሩ ኢቲ 302 የሆነው አውሮፕላኑ 149 መንገደኞችንና ስምንት የበረራ ሰራተኞችን አሳፍሮ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ከ44 ደቂቃ ላይ ነበር የተነሳው።