የሀገር ውስጥ ዜና

በሰሜን ሸዋ ዞን መሀል ሜዳ ከተማ በቦምብ ጥቃት የ3 ሰዎች ህይወት አለፈ

By Tibebu Kebede

March 10, 2020

አዲስ አበባ፣መጋቢት 1፣2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን ሸዋ ዞን መሀል ሜዳ ከተማ በአንድ ግለሰብ በተወረወረ ቦምብ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፋን ፖሊስ አስታወቀ።

የከተማ አስተዳደሩ ፓሊስ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ጥላሁን ደበበ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት፥ ድርጊቱ ትናንት ምሽት አንድ ሰዓት አካባቢ በከተማዋ 03 ቀበሌ በሚገኝ አንድ መጠጥ ቤት ነው የተፈጸመው።