Fana: At a Speed of Life!

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አመራሮችና ሠራተኞች የችግኝ ተከላ አካሄዱ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አመራሮችና ሠራተኞች በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር በጉለሌ እጽዋት ማዕከል የችግኝ ተከላ አካሂደዋል።

በችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ የጽህፈት ቤቱ ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ተፈሪ ፍቅሬና ሌሎች አመራሮች ተሳትፈዋል።

አቶ ተፈሪ÷ኢትዮጵያውያን በአረንጓዴ አሻራው የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባና ከችግኝ ተከላው ባሻገር ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ እያደረገች ያለውን የለውጥ ጉዞ መደገፍ ይገባቸዋል ብለዋል።

የተተከሉችግኞችን በመንከባከብ ለታለመው ግብ መሳካት ሁሉም ኃላፊነቱን መወጣት አለበት ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.