Fana: At a Speed of Life!

ሶማሌ ክልል በበጀት ዓመቱ 7 ነጥብ 26 ቢሊየን ብር ገቢ መሠብሰብ መቻሉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2014(ኤፍ ቢ ሲ) ሶማሌ ክልል በ2014 በጀት ዓመት ከገቢ ግብር 7 ነጥብ 26 ቢሊየን ብር መሰብሰብ መቻሉን የሶማሌ ክልል ርዕሰ-መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ገለጹ፡፡

ክልሉ በበጀት ዓመቱ በድርቅ እና በሌሎች ችግሮች በመፈተኑ ለመሰብሰብ ያቀደውን 7 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ገቢ ግብር ማሳካት እንዳላስቻለ የተገለጸ ሲሆን፤ የዕቅዱን 95 ነጥብ 5 በመቶ አፈጻጸም ማለትም 7 ነጥብ 26 ቢሊየን ብር ግን መሠብሰብ እንደቻለ አቶ ሙስጠፌ መሀመድ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አመላክተዋል፡፡

አቶ ሙስጠፌ ÷ ባለፉት አራት የለውጥ ዓመታት ብቻ 18 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ገቢ እንደ ተሰበሰበ የጠቆሙ ሲሆን ይህም ከለውጡ በፊት ከነበሩት 10 ዓመታት የ10 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል፡፡

ሁኔታው የክልሉ መንግስት የመፈጸም አቅም መጠናከሩን እንደሚያሳይ አያየዘው ገልፀዋል።

እየተካሄደ ባለው የክልሉ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሥራ አፈፃፀም ግምገማ ላይ የክልሉ የገቢዎች ቢሮ የአፈፃፀም ሪፖርት ቀርቧል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.