የሀገር ውስጥ ዜና

በማምረቻና ኮንስትራክሽን ዘርፍ ውዝፍ እዳ ላለባቸው ግብር ከፋዮች ቅጣታቸው እንዲነሳ መደረጉ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

March 10, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በማምረቻ እና ኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ውዝፍ እዳ ያለባቸው ግብር ከፋዮች ቅጣታቸው ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ በማድረግ ለችግሮቻቸው መፍትሄ መሰጠቱን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዘርፉ የተሰማሩ ባለሃብቶች ከግብር አወሳሰን ጋር ተያይዞ ያለባቸውን ውዝፍ እዳ አከፋፈል በተመለከተ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ሲያቀርቡ መቆየታቸው የተገለፀ ሲሆን፥ ለዚህም ሚኒስቴሩ ችግሮቹን በትኩረት በመመልከት መፍትሄ መስተጡን ነው ያስታወቀው።