ስፓርት

አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ ዛሬ ምሽት ሊያደርጉት የነበረው ጨዋታ ተራዘመ

By Tibebu Kebede

March 11, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ ዛሬ ምሽት ሊያደርጉት የነበረው ተጠባቂ ጨዋታ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተራዘመ።

ጨዋታው የተራዘመው የግሪኩ እግር ኳስ ክለብ ኦሊምፒያኮስ ባለቤት ኢቫንጄሎስ ማሪናኪስ በትናንትናው ዕለት በተደረገላቸው ምርመራ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን ተከትሎ ነው።