አቶ ሽመልስ አብዲሳ በቢሾፍቱ የከተማ ግብርና ሥራዎችን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ ከፍተኛ የክልሉ መንግሥት ሥራ ኃላፊዎች በቢሾፍቱ ከተማ ተገኝተው የከተማ ግብርና ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዚሁ ጊዜ ባደረጉት ንግግር÷ የክልሉ መንግስት በአራት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ ጠቅሰው፥ እነሱም በከተማ ግብርና እና የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ ፣ ፣ የፈጠራና ክህሎትን ማበረታታት እንዲሁም የአገልግሎት ዘርፍን መማፋን መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም ÷ በአዲስ ጉልበት ለከተማ ግብርና ትኩረት በመስጠት የብልጽግና ጉዟችንን እናረጋግጣለንም ነው ያሉት፡፡
በአቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራው ልዑክ በቢሾፍቱ ከተማ በነበረው ቆይታ የከተማ የዶሮ እርባታ፣ የወተት ከብቶችንና የአሳማ እርባታ ፣ የንብ ማነብ እና የማር ምርት፣ የአትክልት ማዳበሪያ ዝግጅት ስራዎችን መጎብኘቱም ኦቢኤን ዘግቧል፡፡