የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል ለኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች 22 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ብድር ተሰጠ

By Feven Bishaw

July 21, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2014 በጀት ዓመት በአማራ ክልል የሚገኙ የግልና የመንግስት ባንኮች በተለያዩ የብድር ሞደሊቲዎች 22 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር ብድር ለኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች መሰጠታቸው ተገለፀ፡፡

ለረዥም ጊዜ የክልሉ ችግር ሆኖ የቆየው የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መሻሻል እያሳየ መምጣቱ ተገልጿል፡፡