Fana: At a Speed of Life!

አሜሪካ በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ወገኖች የሚውል 488 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ አደረገች

 

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ በድርቅ ምክንያት ለተጎዱ ዜጎች የሚውል የ488 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ይፋ አድርጓል።

በኢትዮጵያ የአሜሪካ መንግሥት ጉዳይ ፈጻሚ አምባሳደር ትሬሲ አን ጃኮብሰን የሰብዓዊ ድጋፋን በማስመልከት ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም÷ ድጋፉ በድርቅ ምክንያት አፋጣኝ ሰብዓዊ ድጋፍ ለሚሹ 4 ነጥብ 8 ሚሊየን ዜጎች የሚውል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አስቸኳይ የምግብ ድጋፍና የተመጣጠነ ምግብ ለሕጻናት እንደሚቀርብ በመግለጫው መነሳቱን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision

ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.