አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የሰብአዊ እርዳታ ሟጓጓዝ መጀመሩን አስታወቀ፡፡
ተቋሙ በትዊተር ገፁ እንዳስታወቀው ፥ ሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተሽከርካሪዎች በዋግኽምራ ዞን በሚገኙት አበርገሌ፣ ፃግብጂ እና ዝቋላ ወረዳዎች እየተጓጓዙ መሆኑን ገልጿል፡፡
የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ከሌሎች አደጋዎች የከፋ መሆኑን የገለፀው ተቋሙ ፥ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦቶች መቀጠል እንዳለባቸውም አስገንዝቧል፡፡