Fana: At a Speed of Life!

የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ለአትሌቲክስ ቡድናችን አቀባበል ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቀረበ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብኃይል ለአትሌቲክስ ቡድናችን አቀባበል ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል፡፡
በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ደማቅ ውጤት ላስመዘገበው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ የልዑካን ቡድን አባላት አቀባበል ሲባል ለተሸከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብኃይል ይፋ አድርጓል፡፡
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ የሚገባ ሲሆን÷ ለቡድኑ ደማቅ አቀባበል እንደሚደረግ የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡
በአቀባበሉ ወቅት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚደረጉ ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ ግብረ ኃይሉ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ለአትሌቲክስ ቡድኑ አባላት ሐምሌ 21 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ደማቅ አቀባበል የሚደረግ ሲሆን÷ የአትሌቲክስ ቡድኑ ካረፈበት ስካይላይት ሆቴል ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ በአጀብ በአዲስ አበባ ከተማ ዋና ዋና ጎዳናዎች ስለሚጓዝ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ ግብረ ኃይሉ ማስታወቁን የአዲስ አበባ ፖሊኮሚሽን መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.