የሀገር ውስጥ ዜና

ሚኒስቴሩ የክረምት የበጎ ፈቃድ መርሐ ግብሩን በሲዳማ ክልል አስጀመረ

By Feven Bishaw

July 29, 2022

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የትራስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የክረምት የበጎ ፈቃድ መርሐ ግብሩን ዛሬ በሲዳማ ክልል ወንዶ ገነት ወረዳ አስጀምሯል።

የትራስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዳግማዊት ሞገስ መርሐ ግብሩን በወረዳው በሚገኘው የወንዶገነት ዎሻ አንደኛ እና መለስተኛ ሁለተኛ ትምህርት ቤቶች አስጀምረዋል።